ÐÓMAPµŒºœ

ፍልስጀማውያን በካን ዮኒስ ኹተማ በሚገኘው ዚማህበሚሰብ በጎ አድራጊ ምግብ አቅራቢ ቡድኖቜ  ዹተዘጋጀ ምግብ ለመቀበል ተሰብስበው ፍልስጀማውያን በካን ዮኒስ ኹተማ በሚገኘው ዚማህበሚሰብ በጎ አድራጊ ምግብ አቅራቢ ቡድኖቜ ዹተዘጋጀ ምግብ ለመቀበል ተሰብስበው 

ዚመብት ተሟጋቜ ቡድኖቜ እስራኀል ወደ ጋዛ ዹሚደርሰውን እርዳታ ዹማቋሹጧን ተግባር 'ዚሚሃብ ፖሊሲ' በማለት ገለጹ

ዹዾ§ˆˆáˆ ምግብ ፕሮግራም እስራኀል ወደ ጋዛ ዹሚደርሰውን ሰብዓዊ እርዳታ በማገዷ ምክንያት በጋዛ ያለው ዚምግብ ክምቜቱ ለሁለት ሳምንታት ብቻ እንደሚቆይ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ ድርጅቱ ኚሁለት ሳምንት በፊት ዹተቋሹጠውን ድጋፍ ለማቅሚብ ምግብ ዚጫኑ 14 ተሜኚርካሪዎቜ ወደ ሰሜናዊ ጋዛ ቢልክም እንዳይገባ መኹልኹሉን አስታውቋል።

  አቅራቢ ዘላለም ኃይሉ ፥ አዲስ አበባ

ዹዾ§ˆˆáˆ ምግብ ፕሮግራም ምግብ ዚጫኑ 14 ተሜኚርካሪዎቜ ወደ ሰሜናዊ ጋዛ ቢልክም ተሜኚርካሪዎቹ በዋዲ ጋዛ ዚፍተሻ ጣቢያ ለሶስት ስዓታት ኚቆዩ በኋላ እንዲመለሱ መደሹጉን ዹጠቆመው ተቋሙ፥ በርካታ ሰዎቜ ተሜኚርካሪዎቹን አስቁመው ኹ200 ቶን በላይ ምግብ መዝሹፋቾውን ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ዚአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ ልዑክ ስቲቭ ዊትኮፍ ያቀሚቡትን ዹጋዛን ዚመጀመሪያውን ምዕራፍ ማራዘም ሐማስ አለመቀበሉ ይህንን ዚእርዳታ እገዳ እርምጃ እንዲወስዱ እንዳደሚጋ቞ው ዚእስራኀል ጠቅላይ ሚንስ቎ ቀኒያሚን ኔታንያሁ ገልጞዋል። ሐማስ ሁለተኛው ምዕራፍ ተግባራዊ እንደሚደሚግ ዋስትና ኚአሞማጋዮቹ ካላገኘ አንደኛው ምዕራፍ እንዲራዘም አልስማማም ብሏል።

እስራኀል በጋዛ ሙሉ ዚሰብዓዊ እርዳታ እንዲቋሚጥ ያደሚገቜው በአሜሪካ ዹቀሹበው ዹጋዛ ዚተኩስ አቁም አንደኛ ምዕራፍ ዚማራዘም ሃሳብ ሐማስ አለመቀበሉን ተኚትሎ ነው።

ዚተባበሩት መንግስታት ዚእርዳታ ድርጅቶቜ አስ቞ኳይ ዚተኩስ አቁም ስምምነት ተደርሶ ዚሰብአዊ ድጋፍ በብዛት እንዲገባ ቢጠይቁም ተፋላሚዎቹ እስካሁን ስምምነት ላይ አልደሚሱም።

በሚመዳን ጟም መጀመሪያ ይደሚሳል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበት ዹነበሹው ዚተኩስ አቁም ድርድርም በካይሮ ያለ እስራኀል ተሳትፎ እዚተካሄደ መሆኑ ተገልጿል።
ዚእስራኀል ጠቅላይ ሚኒስትር ሃማስን ዚእስራኀል-ሃማስ ዚተኩስ አቁም ስምምነትን ለማራዘም አሜሪካ ያቀሚበቜውን ሀሳብ ውድቅ አድርጓል በማለት እና ዚምግብ አቅርቊቶቜን ዘርፏል በሚል እርዳታ ወደ ጋዛ እዳይገባ መኹልኹላቾውን ተኚትሎ በጋዛ ሰርጥ ላይ ዚምግብ ዋጋ በኹፍተኛ ሁኔታ መጚመሩን እና ዚማህበሚሰብ ምግብ አቅራቢ ድርጅቶቜ ክምቜት መሟጠጡን ዘገባዎቜ እያሳዩ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ቀንያሚን ኔታንያሁ ሐማስ ዚእርዳታ አቅርቊቱን በመስሚቅ “ዚሜብር ተግባሩን” ለመደገፍ እዚተጠቀመበት ነው ሲሉ ወንጅለው ማንኛውም እርዳታ እንዳይገባ እግድ ጥለዋል።

ሐማስ በበኩሉ እስራኀል ዚተኩስ አቁሙን ለማደናቀፍ እዚወሰደቜው ያለው እርምጃ እንደሆነ እና ድርጊቱ “ዹጩር ወንጀል እንደሆነ” እና “በተኩስ አቁሙ ላይ ዚተካሄደ ቀጥተኛ ጥቃት ነው” ሲል ኚሷል።

እስራኀል 2 ሚሊዮን ለሚሆነው ዹጋዛ ህዝብ ይደርስ ዹነበሹውን ዚምግብ፣ ዚነዳጅ፣ ዚመድሃኒት እና ሌሎቜ አቅርቊቶቜን ማቋሹጧ በአኚባቢው ዹዋጋ ንሚት እንዲኚሰት ማድሚጉን እና በአሁኑ ወቅት ሰብአዊ እርዳታ ዚሚያቀርቡ ቡድኖቜ እዚመነመነ ካለው ክምቜቶቻ቞ው በመውሰድ በጣም ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎቜ ለማሰራጚት እዚሞኚሩ እንደሆነ ተገልጿል።

ወደ ሰርጡ ዚሚገባው ዕርዳታ በመቆሙ ምክንያት ዚሚድኀት ሰራተኞቹ እስራኀል እና ሃማስ ጥር ወር ላይ ባደሚጉት ዚተኩስ አቁም ስምምነት ምዕራፍ አንድ ላይ በነበሩት ስድስት ሳምንታት ሚሃብን ለመታደግ ሲያደርጉት ዹነበሹውን ጥሚት እንዳጚናገፈባ቞ው አሳውቀዋል።

ዚተኩስ አቁሙ ለ15 ወራት ዹዘለቀውን ዹጋዛ ደም አፋሳሜ ጊርነት ያስቆመ ሲሆን፥ በዚህም 33 እስራኀላዊ ታጋ቟ቜ እንዲሁም በእስራኀል እስር ቀት ያሉ 1 ሺህ 900 ፍልስጀማውያን ተለቀዋል።

ለ16 ወራት በላይ እዚተካሄደ ባለው ጊርነት ምክንያት ዹጋዛ ህዝብ ሙሉ በሙሉ በጭነት መኪና ተጭነው በሚገቡ ምግቊቜ እና ሌሎቜ እርዳታዎቜ ላይ ዹተመሰሹተ እንደሆነ ዚሚታወቅ ሲሆን፥ አብዛኛው ህዝብ ኚመኖሪያ ቀቱ በመፈናቀሉ ምክንያት ጊዜያዊ መጠለያ እደሚያስፈልገው ዚሚድኀት ሰራተኞቜ ገልጞዋል። ኹዚህም በተጚማሪ ነዳጅ ዚሚያስፈልገው ዚጭነት መኪናዎቜ እርዳታ እንዲያደርሱ ለማስቻል ብቻ ሳይሆን ሆስፒታሎቜ፣ ዹውሃ ፓምፖቜ፣ ዳቊ ቀቶቜ እና ዚ቎ሌኮሙኒኬሜን አገልግሎቶቜን ለማስቀጠል ጭምር እንደሆነ ተገልጿል።

እስራኀል ዚእገዳው እና ኚበባው ዋና ዓላማ ሃማስ ዚዩናይትድ ስ቎ትስን ዚተኩስ አቁም ዚማራዘሚያ ሃሳብ እንዲቀበል ግፊት ማድሚግ እንደሆነ እዚገለጞቜ ሲሆን፥ እስራኀል ኚሃማስ ጋር ዚገባቜውን ዚዕርዳታ ፍሰቱ እንዲቀጥል ዚሚያስቜለውን ዹሁለተኛ ምዕራፍ ዚተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ ለማድሚግ እንደዘገዚቜ ተነግሯል።

‘ዚሚሃብ ፖሊሲ’
ዚእስራኀሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቀንያሚን ኔታንያሁ ማክሰኞ ዕለት እንደተናገሩት በሃማስ ላይ ዚሚያደርጉትን ጫና አጠናክሹው ለመቀጠል መዘጋጀታ቞ውን ገልጞው፥ ሃማስ በተኩስ አቁም ስምምነቱ ኚተስማማ ወደ ጋዛ ዚሚገባውን ዚኀሌክትሪክ ሃይል እንደማያቋርጡ ቃል ገብተዋል።

ዚመብት ተሟጋቜ ቡድኖቜ እስራኀል በጋዛ ዚሰብአዊ ድጋፍ ተደራሜነት ዙሪያ ዚያዘቜውን አቋም “ዚሚሃብ ፖሊሲ” ብለው ዚገለጹ ሲሆን፥ ዚጊዜያዊ ዚተኩስ አቁም ስምምነቱ ጊዜ ካለቀ ኚአራት ቀናት በኋላ ዚተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ዚምግብ ኀጀንሲ ዹሆነው ዹዾ§ˆˆáˆ ምግብ ፕሮግራም እንደገለጞው በምዕራፍ አንዱ ዚተኩስ አቁም ስምምነት ወቅት ሁሉንም ዚእርዳታ ምግብ ለተራቡ ሰዎቜ በማኹፋፈል ላይ ትኩሚት አድርጎ ስለነበሚ በአሁኑ ወቅት በጋዛ በቂ ዹሆነ ዚመጠባበቂያ ምግብ ክምቜት እንደሌለው በመግለጜ፥ አሁን ያሉት ክምቜቶቜ ለዳቊ መጋገሪያዎቜ እና ምግብ አብሳይ ቡድኖቜ ኚሁለት ሳምንታት ላነሰ ጊዜ ብቻ አገልግሎታ቞ውን እንዲቀጥሉ ለማድሚግ በቂ ናቾው ብሏል።

ዹኖርዌይ ዚስደተኞቜ ምክር ቀት በበኩሉ እንደገለጞው፣ በጋዛ ውስጥ ምንም ዓይነት መጠባበቂያ ዚድንኳን ክምቜት እንደሌለው በመግለጜ፥ በምዕራፍ አንዱ ዚተኩስ አቁም ስምምነት ወቅት ላይ ዚገቡት ዚመጠለያ ቁሳቁሶቜ በቂ እንዳልነበሩ አመልክቷል።

ዚድርጅቱ ዚኮሚዩኒኬሜን ኃላፊ እንደተናገሩት ክምቜቱ በቂ ቢሆን ኖሮ “በመጠለያ ቁሶቜ እና ብርድ ልብሶቜ እንዲሁም ተገቢ ዹህክምና መሳሪያዎቜ እጥሚት ዚተነሳ ዚሚሞቱ ጹቅላ ህጻናት አይኖሩም ነበር” በማለት ዚቜግሩን አሳሳቢነት ገልጞዋል።
 

06 Mar 2025, 12:27