MAP

ር.ሊ.ጳ ሊዮ የሕይወታችንን ሀብት በፍቅር እና በምሕረት ውስጥ ፈሰስ እናድርግ ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዩ 14ኛ በነሐሴ 04/2017 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ ሥርዓተ አምልኮ ላይ በተነበበውና "በምድር ላይ ሀብት ማከማቸት እንደማይገባ" በሚገልጸው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው አስተንትኖ ማድረጋቸው የተገለጸ ሲሆን በዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባደርጉት አስተንትኖ የሕይወታችንን ሀብት በፍቅር እና በምሕረት ውስጥ ፈሰስ ማድረግ ይኖርብናል ማለታቸው ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በወቅቱ ያደርጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ መልካም እለተ ሰንበት ይሁንላችሁ!

በዛሬው ወንጌል ኢየሱስ ሕይወታችን የሆነውን ሀብት እንዴት መጠቀም እንደሚገባን እንድናስብ ጋብዞናል (ሉቃስ 12፡32-48)። “ንብረታችሁን ሽጡ ምጽዋትንም ስጡ” (ሉቃስ 12፡33) ይላል።

እግዚአብሔር የሰጠንን ስጦታዎች ለራሳችን ብቻ ጠብቀን እንዳንይዝ ይልቁንም ለሌሎች በተለይም የእኛን እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው በልግስና እንድንሰጥ ይመክረናል። ያለንን ቁሳዊ እቃዎች መጋራት ብቻ ሳይሆን ክህሎታችንን፣ ጊዜያችንን፣ ፍቅራችንን፣ መገኘትን እና ርህራሄን ለሌሎች አገልግሎት መስጠት ነው። ባጭሩ፣ እያንዳንዳችንን በዋጋ ሊተመን የማይችል እና የማይደገም መልካም፣ ሕያው ንብረት የሚያደርገን በእግዚአብሔር እቅድ ውስጥ ያለው ነገር ሁሉ ማልማት እና ለማደግ መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ መደረግ አለበት። ያለበለዚያ እነዚህ ስጦታዎች ይደርቃሉ እና ዋጋቸው ይቀንሳል፣ ወይም እንደ ሌባ የሚነጥቀው በቀላሉ የሚበላ ነገር አድርገው የሚወስዱት ይሆናሉ።

እኛ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ነን፣ የእግዚአብሔር ስጦታ ደግሞ በዚህ መንገድ ጥቅም ላይ መዋል አለበት። ወደ ሙላት ለመምጣት እና ራሳችንን ለመግለጽ ቦታ፣ ነፃነት እና ግንኙነቶች እንፈልጋለን። ሁሉንም የህልውናችንን ገፅታዎች የሚቀይር እና የሚያጎናጽፍ ፍቅር እንፈልጋለን። ኢየሱስ እነዚህን ቃላቶች የተናገረው ወደ እየሩሳሌም በሚወስደው መንገድ ላይ ሳለ፣ ራሱን በመስቀል ላይ ለደህንነታችን በሚያቀርብበት ወቅት ያለምክንያት የተናገራቸው ቃላት አይደሉም።

የምሕረት ሥራዎች የመኖራችንን ሀብት አደራ የምንሰጥበት እጅግ አስተማማኝ እና ትርፋማ ባንክ ናቸው፤ ምክንያቱም በዚያ፣ ወንጌሉ እንደሚያስተምረን፣ “በሁለት ትናንሽ የመዳብ ሳንቲሞች” ድሃዋ መበለት እንኳ በዓለም ላይ እጅግ ባለጸጋ ትሆናለች (ማር. 12፡41-44)።

በዚህ ረገድ ቅዱስ አውግስጢኖስ እንዲህ ይላል፡- “አንድ የመዳብ ሳንቲም ሰጥተህ አንድ የብር ሳንቲም ከተቀበልክ እና አንድ የወርቅ ሳንቲም ከተቀበልክ በዕድልህ ደስ ይልሃል፤ የሰጠኸው ነገር በእርግጥ ይለወጣል፤ ወርቅ ሳይሆን ብር ሳይሆን የዘላለም ሕይወት ወደ አንተ ይመጣል” ይላል። እናም ለምን እንደሆነ ያብራራል፦ "እሱ ይለወጣል፣ ምክንያቱም አንተ ራስህ ትለወጣለህ" በማለት ተናግሯል።

በዚህ ምን ማለቱ እንደሆነ ለመረዳት ልጆቿን የምታቅፍ እናት ማሰብ እንችላለን፡ በዓለም ላይ ካሉት ሁሉ በጣም ቆንጆ እና ባለጸጋ አይደለችምን? ወይም የወንድ ጓደኛ እና የሴት ጓደኛ አብረው ሲሆኑ እንደ ንጉስ እና ንግሥት እንደ ሆኑ አይሰማቸውምን? ሌሎች ብዙ ምሳሌዎችን ልናስብ እንችላለን።

ስለዚህ፣ የትም ብንሆን፣ በቤተሰብ፣ በደብራችን፣ በትምህርት ቤት ወይም በሥራ ቦታ፣ በፍቅር ለመንቀሳቀስ ማንኛውም ዕድል እንዳያመልጠን መሞከር አለብን። ይህ ኢየሱስ ከእኛ የሚጠይቀው የንቃት ዓይነት ነው፡ እርስ በእርሳችን የመተሳሰብ፣ ዝግጁ እና ተቆርቋሪ የመሆን ልማዳችንን እንድናሳድግ፣ እርሱ ከእኛ ጋር በእያንዳንዱ ጊዜ  አብሮን ይጓዛል።

እህቶቼ እና ወንድሞቼ፣ ይህንን ፍላጎት እና ኃላፊነት ለማርያም አደራ እንስጥ፡ እሷ የማለዳ ኮከብ፣ ብዙ መለያየት በሚታይበት አለም የምሕረት እና የሰላም ጠባቂዎች እንድንሆን ትርዳን።

11 Aug 2025, 09:46

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >